ክፍለ ጊዜ 17/21

ገጽ 8/9 የሥራ ዕቅድ

የሥራ ዕቅድ

ከጎዳና ተዳዳሪ ህጻናት ጋር በተያያዘ ያላችሁን ተሞክሮ እና በአካባቢያችሁ ያለውን ሁኔታ መሠረት በማድረግ ከዚህ ክፍለ ጊዜ ውስጥ ለእናንተ በጣም አስፈላጊ የሆነው ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ማተኮር ትችላላችሁ። እባካችሁ በሚከተሉት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማን፣ እንዴት፣ የት እና መቼ እንደሚሰራ ተወያዩ እንዲሁም ጻፉ፡-

  • ወደ እንክብካቤ ከመሸጋገር ጋር በተያያዘ የመልሶ ማገገሚያ ሰራተኞች እና የአደራ አሳዳጊዎች እንዴት አብረው መሥራት እንደሚችሉ?
  • የጎዳና ተዳዳሪ ህጻናት ስለሚያሳዩአቸው መተማመን በጎደለው መልኩ ሰውን የመቅረብ ባህርያት እና ሰውን የመቅረብ ችግር ካለባቸው ህጻናት ጋር እንዴት መገናኘት እንደሚቻል ይበልጥ መማር? (እባካችሁ ከፌርስታርት /Fairstart/ ፕሮግራም ውስጥ ክፍለ ጊዜ 5 እና 6ን ተመልከቱ)።
  • የጎዳና ማህበረሰቡ ውስጥ የግንኙነት መረብ እንዴት እንደምንመሰርት ማቀድ?
  • እምነትን መሠረት ካደረጉ እና ማህበረሰብን መሠረት ካደረጉ ሌሎች ድርጅቶች እንዴት የመንፈስ መነሳሳትን ማግኘት እና አብረናቸው መሥራት እንደምንችል ማቀድ።
  • በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን ግንዛቤ እንዴት ማሳደግ እንደምንችል እና ስለ የጎዳና ተዳዳሪ ህጻናት አዎንታዊ አመለካከት መፍጠር እንደምንችል ማቀድ?

    ለጎዳና ተዳዳሪ ህጻናት እንክብካቤ ከማድረግ ጋር በተያያዘ ለምትሰሩት የሚደነቅ ሥራ  ኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች እና  ፌርስታርት (Fairstart) ያለን ሰዎች መልካም ዕድልን እንመኝላችኋለን!